Telegram Group & Telegram Channel
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (18)

13. ንግግርህ ብቁ ይሁን (ሐ)

4. ስለ ማታወቀው ነገር አትናገር

“ውኃ ዋናና ትዳር በምክር አይታወቅም” ይባላል ። ገብተህ ማየት አለብህ ማለት ነው ። ስለ ትዳር ግን አብዝቶ የመከረው ከጴጥሮስ ይልቅ ድንግል ጳውሎስ ነው ። ስለማታውቀው ነገር መጻሕፍትን አገላብጥ ፣ አዋቂዎችን ጠይቅ ። ሁሉን አውቃለሁ ማለት እኔ እግዚአብሔር ነኝ ብሎ እንደ መናገር ነው ። ምንም የማናውቅ ደግሞም ሁሉን የምናውቅ ሆነን አልተፈጠርንም ። እግዚአብሔር ለማንም ጸጋን ጠቅልሎ በጅምላ አልሰጠም ። አንዱ አንዱን እንዲፈልግ እውቀትና ጸጋ ተከፋፍሎ ተሰጥቷል ። የመረጃ እውቀት ለፍላፊ ፣ የሥነ ልቡና እውቀት ብልጥ ሊያደርጉህ ይከጅላሉና ጠንቃቃ ሁን ። መለፍለፍ ከፊት እውቀት ፣ ከኋላ ተግባር የለውም ። የኳስ ተጨዋችን ደመወዝ ማወቅ እውቀት ሳይሆን የቤት ኪራይ ለሌለን ድሆች ተራ ነገር ነው ። እነ እገሌ ተዋጉ ማለት ዜና እንጂ እውቀት አይደለም ። ምናልባት በዚያ አካባቢ ጉዞ ቢኖረን ለጥንቃቄ ይረዳል ። ብዙ የማናውቃቸው ነገሮች አሉ ። አውቀናቸውም ገና የሚሻሩ እውቀቶች አሉ ። በየጊዜው ሳይንሱ ራሱን እያደሰ ፣ ከሃምሳ ዓመት በፊት የመጨረሻ ያለውን እውቀት አሁን ላይ ስህተት ነበረ እያለ ነው ። ሁሉን የሚያውቁ የሚመስላቸው ሰዎች ሊሮጡ ይችላሉ ፣ ግን የሚያጠፉት ይበዛል ። ጸጋን ለባለጸጋው መተው ጊዜን ፣ ገንዘብን ፣ ሰውን ማትረፊያ ነው ። አንተ ግን ስለሁሉም ነገር አስተያየት አትስጥ ። አላዋቂ ሲናገር የተሳሳተ መረጃ መስጠቱ ብቻ ሳይሆን ሊቃውንትን ዱዳ ያደርጋቸዋል ። ዘመኑ የጆሮ ጠገቦች ነው ፣ እኛ በራችንን እንዝጋ ይላሉ ።

5. ከተናደድህ አትናገር

ፍሬኑ የተበጠሰ መኪና በትራፊክ ምልክት አይቆምም ። የሚቆመው ተጋጭቶ ወይም ተገልብጦ ነው ። ንዴትም ፍሬኑ የተበጠሰ መኪና መሆን ነው ። ንዴት እውቀትህን ፣ ለዘመናት ያካበትከውን ስምህን ፣ ወዳጅነትህን ገደል ይዞ የሚገባ ነው ። ውስጥህ እንደ ተበሳጨ ከተሰማህ እዚያ ቦታ ላይ አትቆይ ። ወዲያው ወጥተህ 500 ሜትር ጉዞ አድርግ ። ነፋሱ ሲነካህ ፣ አዲስ ነገር ስታይ ንዴትህ እየበረደ ፣ በትክክል እያሰብህ ትመጣለህ ። በንዴት ሆነህ ከትዳር አጋርህ ጋር አትነጋገር ። ጉዞው ገና ለዕድሜ ልክ ነውና ሁሉን ተናግረህ መጨረስ አያስፈልግህም ። በሥርዓት አለመነጋገር እንጂ የማያግባባ ነገር በዓለም ላይ የለም ። ሰዎች ክፉ የሚናገሩህ ክፉ ስትናገር በአንተ ስህተት ውስጥ ለመደበቅና ፣ አንተን በጸጸት ለማሰቃየት ነው ። ለሰዎች ተንኮል ምቹ አትሁንላቸው ። ቢሆንም በውስጥህ ያለውን ቅንነት የንዴት ቃል ሊሸፍነው ይችላልና ከተናደድህ አትናገር ። ንዴት ዘመድ የሚሆነው በሰዓቱ ብቻ ነው ። ወዲያው ጸጸቱ ይጀምራል ። ከሰዎች ክፋት በላይ የሚያሳስበው አንተን ክፉ እንዳያደርጉህ ነው ።

6. ንግግር አሳማሪ አትሁን

እግዚአብሔር አፈ ቅቤውን አሮንን ሳይሆን አፈ ትቡን ሙሴን እንደመረጠ አስተውል ። ንግግር በሰው ፊት ትልቅ ያሰኝ ይሆናል ። እግዚአብሔር ግን ልብንና ተግባርን ይመዝናል ። በንግግር ቢሆን በዚህ ዘመን ሁሉም አማኝ ነው ። እንዳየነው ግን በእግዚአብሔር የሚያምን ጥቂት ነው ። የዘመኑ የኑሮ ቄንጥ እግዚአብሔር እንዳለ እያወራህ እንደሌለ አድርገህ ኑር የሚል ነው ። የሰሙት ነገር ከጆሮአቸው ወደ ልባቸው ያልወረደ ፣ ምርጥ ቃል ሲያገኙ ይህን ለስብሰባዬ እያሉ የሚጨነቁ አያሌ ናቸው ። በእሳት አለንጋ እየተገረፉ ፣ በገጣሚና በተሳዳቢ የሚዝናኑ ፣ “ልኩን ነገረልኝ” እያሉ አጉል እርካታ የሚረኩ አያሌ ናቸው ። የአገራችንን መከራ ያረዘመው በሞታችን መሳለቃችን ነው ። በሥርዓት መናገር አለብህ ። ነገር ግን ሁሉም ሕይወትህ ንግግር እንደሆነ በማሰብ ስለ ጣፋጭ አገላለጥ አትጨነቅ ። ተግባርህ ካረከሰህ መቼም ቢሆን ንግግርህ አይቀድስህም ። የምትሰማውን ጥቅስ ፣ የምትሰበከውን ስብከት ፣ ያዳመጥከውን ተረት መጀመሪያ አጣጥመው ። ከዚያ በኋላ በቦታው ተናገረው ። ቃለ እግዚአብሔር እንደ እንደ ቆርቆሮ እያጠባቸው የሚሄድ፣ የማይረሰርሱ ሰሚዎችና ተናጋሪዎች አሉ ። እንደ አፈር ቦይ ረክተው ለሌላው ቢለቁ ግን ድነው ያድኑ ነበር ። ሃይማኖተኛና የሚደልልን ሰው መለየት እስኪያቅት አንድ ሆነው እያየን ነው ። እግዚአብሔር ቃሉን ለማስታወቂያ ሠራተኛ ሳይሆን ለምስክር ሰጥቷል ።

በምዕራብ አገሮች ክርስትናው እየጠፋ ያለው በቃላት አሳማሪዎች ስህተት ነው ። ያንን ስህተት ተሸክመው ወደ አገራችን የገቡት የሚስዮናውያንና የአገር አስወራሪዎች ደቀ መዛሙርት ቃላት በማሳመር እግዚአብሔርን የሚያከብሩት ይመስላቸዋል ። አንድ የአእምሮ በሽተኛ የነበሩ ፣ ዕርቃናቸውን የሚዞሩ ሰው እንዲህ እያሉ ይናገሩ ነበር ይባላል፡- “ሰው ሁሉ አብዶ ፣ እኔ ብቻ ቀረሁ ።” ዛሬም ሁሉ ጠፍቷል ፣ እኔ ብቻ ድኛለሁ የሚሉ ፣ በእኛ በኩል ካልሆነ ጌታን አታገኙም እያሉ ቃላት የሚያሳምሩ ለዚህ ትውልድና አገር ትልቅ ዕዳ ይዘው እየመጡ ነው ። ይህ ያልገባው ያገሬ ልጅ ሥነ መለኮትን በቃላት ቁማር እየለወጠ ይነጉዳል ። ካልተመለሰ መጨረሻው እግዚአብሔር የለሽ ሁኖ ይቀራል ። ለዚህም አውሮፓና ሰሜን አሜሪካ ምስክር ናቸው ። እግዚአብሔር በእውነት እንጂ በድለላ አይገኝም ።


ይቀጥላል

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም.



tg-me.com/Nolawii/3927
Create:
Last Update:

የሕይወት ሥነ ሥርዓት (18)

13. ንግግርህ ብቁ ይሁን (ሐ)

4. ስለ ማታወቀው ነገር አትናገር

“ውኃ ዋናና ትዳር በምክር አይታወቅም” ይባላል ። ገብተህ ማየት አለብህ ማለት ነው ። ስለ ትዳር ግን አብዝቶ የመከረው ከጴጥሮስ ይልቅ ድንግል ጳውሎስ ነው ። ስለማታውቀው ነገር መጻሕፍትን አገላብጥ ፣ አዋቂዎችን ጠይቅ ። ሁሉን አውቃለሁ ማለት እኔ እግዚአብሔር ነኝ ብሎ እንደ መናገር ነው ። ምንም የማናውቅ ደግሞም ሁሉን የምናውቅ ሆነን አልተፈጠርንም ። እግዚአብሔር ለማንም ጸጋን ጠቅልሎ በጅምላ አልሰጠም ። አንዱ አንዱን እንዲፈልግ እውቀትና ጸጋ ተከፋፍሎ ተሰጥቷል ። የመረጃ እውቀት ለፍላፊ ፣ የሥነ ልቡና እውቀት ብልጥ ሊያደርጉህ ይከጅላሉና ጠንቃቃ ሁን ። መለፍለፍ ከፊት እውቀት ፣ ከኋላ ተግባር የለውም ። የኳስ ተጨዋችን ደመወዝ ማወቅ እውቀት ሳይሆን የቤት ኪራይ ለሌለን ድሆች ተራ ነገር ነው ። እነ እገሌ ተዋጉ ማለት ዜና እንጂ እውቀት አይደለም ። ምናልባት በዚያ አካባቢ ጉዞ ቢኖረን ለጥንቃቄ ይረዳል ። ብዙ የማናውቃቸው ነገሮች አሉ ። አውቀናቸውም ገና የሚሻሩ እውቀቶች አሉ ። በየጊዜው ሳይንሱ ራሱን እያደሰ ፣ ከሃምሳ ዓመት በፊት የመጨረሻ ያለውን እውቀት አሁን ላይ ስህተት ነበረ እያለ ነው ። ሁሉን የሚያውቁ የሚመስላቸው ሰዎች ሊሮጡ ይችላሉ ፣ ግን የሚያጠፉት ይበዛል ። ጸጋን ለባለጸጋው መተው ጊዜን ፣ ገንዘብን ፣ ሰውን ማትረፊያ ነው ። አንተ ግን ስለሁሉም ነገር አስተያየት አትስጥ ። አላዋቂ ሲናገር የተሳሳተ መረጃ መስጠቱ ብቻ ሳይሆን ሊቃውንትን ዱዳ ያደርጋቸዋል ። ዘመኑ የጆሮ ጠገቦች ነው ፣ እኛ በራችንን እንዝጋ ይላሉ ።

5. ከተናደድህ አትናገር

ፍሬኑ የተበጠሰ መኪና በትራፊክ ምልክት አይቆምም ። የሚቆመው ተጋጭቶ ወይም ተገልብጦ ነው ። ንዴትም ፍሬኑ የተበጠሰ መኪና መሆን ነው ። ንዴት እውቀትህን ፣ ለዘመናት ያካበትከውን ስምህን ፣ ወዳጅነትህን ገደል ይዞ የሚገባ ነው ። ውስጥህ እንደ ተበሳጨ ከተሰማህ እዚያ ቦታ ላይ አትቆይ ። ወዲያው ወጥተህ 500 ሜትር ጉዞ አድርግ ። ነፋሱ ሲነካህ ፣ አዲስ ነገር ስታይ ንዴትህ እየበረደ ፣ በትክክል እያሰብህ ትመጣለህ ። በንዴት ሆነህ ከትዳር አጋርህ ጋር አትነጋገር ። ጉዞው ገና ለዕድሜ ልክ ነውና ሁሉን ተናግረህ መጨረስ አያስፈልግህም ። በሥርዓት አለመነጋገር እንጂ የማያግባባ ነገር በዓለም ላይ የለም ። ሰዎች ክፉ የሚናገሩህ ክፉ ስትናገር በአንተ ስህተት ውስጥ ለመደበቅና ፣ አንተን በጸጸት ለማሰቃየት ነው ። ለሰዎች ተንኮል ምቹ አትሁንላቸው ። ቢሆንም በውስጥህ ያለውን ቅንነት የንዴት ቃል ሊሸፍነው ይችላልና ከተናደድህ አትናገር ። ንዴት ዘመድ የሚሆነው በሰዓቱ ብቻ ነው ። ወዲያው ጸጸቱ ይጀምራል ። ከሰዎች ክፋት በላይ የሚያሳስበው አንተን ክፉ እንዳያደርጉህ ነው ።

6. ንግግር አሳማሪ አትሁን

እግዚአብሔር አፈ ቅቤውን አሮንን ሳይሆን አፈ ትቡን ሙሴን እንደመረጠ አስተውል ። ንግግር በሰው ፊት ትልቅ ያሰኝ ይሆናል ። እግዚአብሔር ግን ልብንና ተግባርን ይመዝናል ። በንግግር ቢሆን በዚህ ዘመን ሁሉም አማኝ ነው ። እንዳየነው ግን በእግዚአብሔር የሚያምን ጥቂት ነው ። የዘመኑ የኑሮ ቄንጥ እግዚአብሔር እንዳለ እያወራህ እንደሌለ አድርገህ ኑር የሚል ነው ። የሰሙት ነገር ከጆሮአቸው ወደ ልባቸው ያልወረደ ፣ ምርጥ ቃል ሲያገኙ ይህን ለስብሰባዬ እያሉ የሚጨነቁ አያሌ ናቸው ። በእሳት አለንጋ እየተገረፉ ፣ በገጣሚና በተሳዳቢ የሚዝናኑ ፣ “ልኩን ነገረልኝ” እያሉ አጉል እርካታ የሚረኩ አያሌ ናቸው ። የአገራችንን መከራ ያረዘመው በሞታችን መሳለቃችን ነው ። በሥርዓት መናገር አለብህ ። ነገር ግን ሁሉም ሕይወትህ ንግግር እንደሆነ በማሰብ ስለ ጣፋጭ አገላለጥ አትጨነቅ ። ተግባርህ ካረከሰህ መቼም ቢሆን ንግግርህ አይቀድስህም ። የምትሰማውን ጥቅስ ፣ የምትሰበከውን ስብከት ፣ ያዳመጥከውን ተረት መጀመሪያ አጣጥመው ። ከዚያ በኋላ በቦታው ተናገረው ። ቃለ እግዚአብሔር እንደ እንደ ቆርቆሮ እያጠባቸው የሚሄድ፣ የማይረሰርሱ ሰሚዎችና ተናጋሪዎች አሉ ። እንደ አፈር ቦይ ረክተው ለሌላው ቢለቁ ግን ድነው ያድኑ ነበር ። ሃይማኖተኛና የሚደልልን ሰው መለየት እስኪያቅት አንድ ሆነው እያየን ነው ። እግዚአብሔር ቃሉን ለማስታወቂያ ሠራተኛ ሳይሆን ለምስክር ሰጥቷል ።

በምዕራብ አገሮች ክርስትናው እየጠፋ ያለው በቃላት አሳማሪዎች ስህተት ነው ። ያንን ስህተት ተሸክመው ወደ አገራችን የገቡት የሚስዮናውያንና የአገር አስወራሪዎች ደቀ መዛሙርት ቃላት በማሳመር እግዚአብሔርን የሚያከብሩት ይመስላቸዋል ። አንድ የአእምሮ በሽተኛ የነበሩ ፣ ዕርቃናቸውን የሚዞሩ ሰው እንዲህ እያሉ ይናገሩ ነበር ይባላል፡- “ሰው ሁሉ አብዶ ፣ እኔ ብቻ ቀረሁ ።” ዛሬም ሁሉ ጠፍቷል ፣ እኔ ብቻ ድኛለሁ የሚሉ ፣ በእኛ በኩል ካልሆነ ጌታን አታገኙም እያሉ ቃላት የሚያሳምሩ ለዚህ ትውልድና አገር ትልቅ ዕዳ ይዘው እየመጡ ነው ። ይህ ያልገባው ያገሬ ልጅ ሥነ መለኮትን በቃላት ቁማር እየለወጠ ይነጉዳል ። ካልተመለሰ መጨረሻው እግዚአብሔር የለሽ ሁኖ ይቀራል ። ለዚህም አውሮፓና ሰሜን አሜሪካ ምስክር ናቸው ። እግዚአብሔር በእውነት እንጂ በድለላ አይገኝም ።


ይቀጥላል

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም.

BY Nolawi ኖላዊ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/Nolawii/3927

View MORE
Open in Telegram


Nolawi ኖላዊ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

For some time, Mr. Durov and a few dozen staffers had no fixed headquarters, but rather traveled the world, setting up shop in one city after another, he told the Journal in 2016. The company now has its operational base in Dubai, though it says it doesn’t keep servers there.Mr. Durov maintains a yearslong friendship from his VK days with actor and tech investor Jared Leto, with whom he shares an ascetic lifestyle that eschews meat and alcohol.

Pinterest (PINS) Stock Sinks As Market Gains

Pinterest (PINS) closed at $71.75 in the latest trading session, marking a -0.18% move from the prior day. This change lagged the S&P 500's daily gain of 0.1%. Meanwhile, the Dow gained 0.9%, and the Nasdaq, a tech-heavy index, lost 0.59%. Heading into today, shares of the digital pinboard and shopping tool company had lost 17.41% over the past month, lagging the Computer and Technology sector's loss of 5.38% and the S&P 500's gain of 0.71% in that time. Investors will be hoping for strength from PINS as it approaches its next earnings release. The company is expected to report EPS of $0.07, up 170% from the prior-year quarter. Our most recent consensus estimate is calling for quarterly revenue of $467.87 million, up 72.05% from the year-ago period.

Nolawi ኖላዊ from cn


Telegram Nolawi ኖላዊ
FROM USA